Enter Keywords: Articles News Forum Posts Downloads Web Links Members
ሿ ሿ! ዳግም ምርጫ!
(የምርጫ ጭውውት ክፍል ሁለት)
ደሞ ምርጫ! ሿ ሿ ዳግም ምርጫ!
አንዋጋም ብለን… ካልን ሰላም ብቻ
እርስ በእርስ መናቆር…ሳናቆም ጥላቻ
ውስጣችን ሳይጠራ…አንቅረብ ለምርጫ!
እስኪ ሰላም ይውረድ!…
እስኪ ውስኪ እንራጭ!…
ካልቻልን አሪንቻታ
ውስኪው ሰላም ይሁን- ፍቅር አሪንቻታ!
ምርጫ ቦርዱ ቢለኝ…አልኩት አላውቀውም
ፍርድ ቤቱስ ሲለኝ…አልኩት አላምነውም
ሰብዓዊ-መብት ሲል…አልኩት አልታደልንም
መከላከያ ሲል…ነገርኩት እንዲል ዝም
ተቃዋሚወችስ ሲል…አልኩት አሳመሙኝ
እየተጣሉ አልኩት…ለምን ብሎ ቢለኝ
ፌደራል ሲጠይቅ…ለሞቴ ፈራሁኝ
ታድያ ዝግጅቱስ?...አልኩት ምንም የለም
ማሸንፉስ ሲለኝ- እሱ አይታሰብም
ታድያ ትርፉስ ሲለኝ- አልኩት አላውቀውም።
ፏ! ፏ! ብሏል መለስ- ፏ! አለ እንጅ በሸገር
መተባበር ጠፍቶ…
መቻቻሉ ጠፍቶ
አገር ትቅደምቀርቶ
ቀና ማሰብ ቀርቶ…. ደግ መስራት ለአገር
ህዝብ ማዳን ቀርቶ…ዘራፍ ማለት ለአገር!
ጠላት ቢደነፋም- ቢበዛ እንቅፋቱ
አይከፋንም ነበር- ለህዝብ መሞቱ
እናንት ሳትስማሙ- ገብታችሁ ለምርጫ
አይፈስም አልልም- የደም አሪንቻታ።
እናንት ልብ ብትሉ- ግለኝነት ቀርቶ
አገር ማዳን ቢሆን- የዘንድሮው “ሞቶ”
ሕዝብ ማዳን ቢሆን- የዘንድሮው ጥረት
ለፍትህ ተታግልን- ለፍትህ ብንሞት
እንኳን አንድ መለስ- በሕዝብ የተተፋ- የጋጠ-ወጥ አውራ
ገፍተን ባስወገድን- ግዙፉን ተራራ
ጣጥሰነው ገብተን….
ድሉን ተቀናጅተን…
በሕዝብ ለሕዝብ የቆመ- መሪያችንን መርጠን
ስላም ብልፅግናን- ገንዝብ ባደረግን።
ዳግማዊ ዳዊት
የካቲት 2002 ዓ.ም.